Skip to main content

ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ

ቢሮው የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩል፣

  1.      የክልሉ መንግስት ፐብሊክ ሰርቪስ ብቃት ያለውና ውጤታማ መሆኑን ያረጋግጣል፣

  2.      የክልል መንግስት ሰራተኞች ምልመላና መረጣ በብቃት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ያደርጋል፣

  3.      የፐብሊክ ሰርቪሱ የሰው ኃይል በቀጣይነት በሚለማበት ጥቅም ላይ የሚውልበትን ስልት ይቀይሳል፣ ተግባራዊነቱንም ይከታተላል፣

  4.     ፐብሊክ ሰርቫንቱ በብቃትና በአፈጻፀም ውጤታማነት ላይ የተመሰረተ የክፍያና የማበረታቻ ሥርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል፣ ውጤታማነቱን ይገመግማል አስፈላገጊውን የማሻሻያ እርምጃ ይወስዳል፣

  5.      የክልል መንግስት ሰራተኞች ሥነ-ምግባር መከታተያ ስርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል፣ አፈጻፀሙን ይከታተላል፣

  6.      የክልል መንግስት ሰራተኞች አስተዳደር ሕጎች በትክክል ስራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላል፣ ያረጋግጣል፣

  7.     የመንግስት ዘርፍ አቅም ግንባታ ስራዎችን ያስተባብራል፣ የመንግስት ዘርፍ አገልግሎት በቀጣይነት የሚሻሻልበትና ውጤታማ የሚሆንበትን ስልት ይቀይሳል ተግባራዊነቱንም ይከታተላል፣ ይገመግማል፣

  8.     የክልል መንግስት መስሪያ ቤቶችን አደረጃጀት አግባብነትን ይመረምራል፣ በአደረጃጀት ማሻሻያ ጥናቶች ላይ አስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል፣

  9.    በክልል መንግስት መስሪያ ቤቶች የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ፣ የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሥርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊ መደረጉን ያረጋግጣል፣

  10.      የፐብሊክ ሰርቪሱ የሰው ሃብት አመራርና የተቋማዊ መረጃዎች ሥርዓት በወጥነት እንዲዳብርና እንዲተገብር ያደርጋል ማዕከላዊ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፣

  11.     የክልሉን የመንግስት መስሪያ ቤቶችን የሰው ሀብት አስተዳደር በበላይነት ይመራል፣ የስራ አመራር መመሪያዎችና የአፈፃፀም መስፈርቶችን ያዘጋጃል ያስፈፅማል፣

  12.      የመንግስት ሰራተኞችን የደመወዝ፣ የልዩ ልዩ አበሎችና ጥቅማ ጥቅሞች ማሻሻያ ያጠናል ሲፈቀድም ስራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፣

  13.      በሕግ መሰረት የክልል መንግስት ሰራተኞችን ከጡረታ ዕድሜ ክልል በላይ በአገልግሎት ላይ ስለማቆየት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ውሳኔ ይሰጣል፣

  14.      በየደረጀው የሚታዩ የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳብነት ችግሮችን በጥናት መለየት፣ ለተለዩ ችግሮች ስልቶች መንደፍ፣ የአፈታት ሂደት መከታተልና መደገፍ፣ የፋይዳ ጥናት በማድረግ የህዝብ እርካታን ማረጋገጥ

  15.       የመንግስት ሠራተኞችን አስተዳደር ፍርድ ቤት ያቋቁማል፣ ያደራጃል፣ አግባብ ባለው ሕግ መሠረት እንዲመራ ያደርጋል

  16.       ዓላማውን ለማስፈፀም የሚረዱ ሌሎች ተግባራትን ያከናውናል፡፡