አቶ ገብሬ ጋጌ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መልዕክት
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ አገልጋይነትን የተላበሰና የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን መሰረት አድርጎ በመስራት የተገልጋዩን እርካታ የሚያረጋግጥ ነፃ፣ገለልተኛና ብቃት ያለዉ ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት በአጠቃላይ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ስርዓት ለመቀየር እየሰራ ይገኛል፡፡
ቢሮዉ ቀጣይነት ባለው መልኩ የሲቪል ሰርቪስ ስርዓቱን ከአዲሱ ትዉልድ የሲቪል ሰርቪስ ፖሊሲ እና ከሃገራዊ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ጋር በተጣጣመ መልኩ በማላመድና በክልሉ በመተግበር የሲቪል ሰርቪስ ስርዓቱን ለዘመናት አንቀዉ ከያዙ ችግሮች በማላቀቅ ዘርፉን ለመቀየር የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ውጤታማ መሆን ይጠበቅበታል፡፡
በመሆኑም ቢሮዉ ቀልጣፋ የተቋማት አደረጃጀት እና የስራ ምዘና ስርዓትን የመዘርጋት፣የመልካም አስተዳደር መርሆዎች ትግበራን የማጠናከር፣ ተዓማኒነት ያለዉ ወቅታዊ የሰዉ ሃይል ስታስቲካል መረጃ የማጠናቀርና ተደራሽ የማድረግ፣የሰዉ ሃብት ህጎች አተገባበር ዉጤታማነትን የማሳደግ፣ ፣በየደረጃው የሚገኙ ተቋማት የአፈፃፀም ውጤታማነትን ማሳደግ እንዲሁም የአፈፃፀም ስራ አመራር ስርዓትን መተግበር ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራቸው ተግባራት ይሆናሉ፡፡ከዚህ በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያን በመተግበር ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት እንዲኖር በማድረግ ዘመናዊ ስርዓት መዘርጋት ይጠበቅበታል፡፡
የለውጥ አመራር ስርዓት የክልሉን የሲቪል ሰርቪስ ስርዓት ግንባታ ቀጣይነት በሚያረጋግጥ አግባብ ከክልሉ አሁናዊ ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራዉ ሥራ ይሆናል፡፡
ለክልላችን መለወጥ ብሎም እንደ ዘርፍ ለሲቪል ሰርቨሱ ስርዓት መቀየር የሁላችንም ተሳትፎ እና ስራ ወሳኝ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር የሲቪል ሰርቪሱን ስርዓት ለመለወጥ በጋራ የየበኩላችንን አስተዋፅኦ እንድናበረክት ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
አቶ ገብሬ ጋጌ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ